EthiopiaRegionsSocial

በነገው እለት የሚከበረውን የአሸንዳ በአል አስመልክቶ በመቀሌ ከተማ የፓናል ውይይት ተካሂዷል።

የፓናል ውይይቱ አብይ አላማ ያለፉት አመታት የበዓሉን አከባበር መገምገም፣አሸንዳን በአለም አቀፍ ደረጃ ስለማስተዋወቅ እንዲሁም ከዩኔስኮ ጋር የተያያዙ ጥናቶች እና ሀሳቦችን ማንሳት ነው ተብሏል፡፡
የትግራይ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ሃላፊ ወ/ሮ ዘነቡ ሐለፎም እንደገለፁት አሸንዳ ከባህላዊ እና ሃይማኖታዊ አንድምታው በተጨማሪ ለሴቶች ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትስስር እንዲሁም ፖለቲካዊ ተሳትፎአቸውን የሚያሳይ የነጻነት ቀን ነው ብለዋል፡፡
በውይይቱ የቀደሙ የአሸንዳ ባህል አከባበርን የሚያሳይ የፎቶግራፍ አውደ ርእይም ተካሂዷል።
ወ/ሮ ዘነቡ ኤርትራዊያን በበዓሉ እንደሚታደሙ ገልጸው በክብረ በዓሉ ስራዎቻቸውን ለማቅረብ ኤርትራዊያን አርቲስቶች ትላንት መቀሌ እንደገቡ ለአርትስ ተናግረዋል፡፡

Show More

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button
Close
Close
Close Bitnami banner
Bitnami