EducationEthiopiaRegionsSocial

አሶሳ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል ተከስቶ የነበረው ግጭት መብረዱን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ

አሶሳ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል ተከስቶ የነበረው ግጭት መብረዱን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ

አርትስ 12/03/2011

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሐይማኖት ዲሳሳ እንደተናገሩት ተፈጥሮ የነበረው ሁከት በመብረዱ ተማሪዎችን ጭምር በማወያየት ችግር ፈጣሪዎቹን ለመለየት እየተሰራነው፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሐይማኖት   እንደገለፁት በትላንትናው ዕለት በሁለት ተማሪዎች መካከል የተከሰተ ግጭት ሰፍቶ  በአጠቃላይ 34 ተማሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

ከተጎጂዎቹ ውስጥ የ 29ኙ ቀላል ጉዳት በመሆኑ ወዲያው ህክምና ተደርጎላቸው ተመልሰዋል፡፡5 ያህሉ ደግሞ በአሶሳ ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል፡፡

የአገር መከላከያ ሰራዊትና የፌደራል ፖሊስም በስፍራው ተገኝተው ግጭቱን እንዳረጋጉት ተሰምቷል፡፡

 

Show More

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button
Close
Close
Close Bitnami banner
Bitnami